tg-me.com/nibab_lehiwot/149
Last Update:
🕊️ሀሙስ 🕊️
ክፍል-4
ምን ብየ ልመልስ ምላሴ ተሳሰረ።ልክ ናቸውኮ ምንም አላውቅም።አንገቴን ደፍቼ ዝም አልኩ.......
ይሄኔ ስለነ አልበርት፣ ስለነ ቶማስ ኤዲሰን ፣ ስለነ ጀምስ ብሩስ ፣ ስለነ አብርሀም ሊንከን ፣ ስለነ ክርስቶፈር ኮሎምበስ .............
ብጠይቅሽ ኖሮ ሁሉንም በትክክል ትመልሽ ነበር አደለም? አሁን ንግግራቸው ወደ ቁጣ እያመራ መጣ።የኔ ልብም እንዲሁ በፀፀት እየደማ መጣ።በእፍረት አንገቴን በ አዎንታ ነቀነቅኩ።
በይ እንጅ ስለነ ቅዱስ ያሬድ ንገሪኝ ፣በይ ስለ ካህኑ ዮቶር አስረጂኝ ፣ በያ ስለ ሊቁ ተዋነይ ተርኪልኝ ፣ቶሎ በይ ስለ ቅዱስ ላሊበላ ንገሪኝ ፣በይ ስለ ህንደኬ ፣ስለ ንጉስ ኢትኤል ፣ስለ ኢትዮጵያዊው ቢላል ፣ስለ ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ፣ ስለ ሔኖክ፣ስለ ባልቻ አብዲሳጋ ፣ስለ ራስ አሉላ...ንገሪኝ..ስለ ንግስተ ሳባ.................በጣም ብዙ የማላውቃቸውን ስሞች ጠሩ።ምንም አላውቅም አልኩኝ።
አየሽ ታዲያ እንዴት ኢትዮጵያዊ ልትባይ ትችያለሽ ኧ?
ንገሪኝ እስኪ እነዚህ ሰወች ድንጋይ ፈልፍለው አለት ጠርበው ህንፃን አነፁ ፣ኢትዮጵን በስልጣኔ አሳደጉ ፣ዜማ ቅኔ ማህሌትን ለአለም አስተማሩ ፣ብራና ፍቀው ቀለም በጥብጠው ፣ የፅሁፍን ጥበብ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአለም አስተማሩ፣ የአመራርን ስርዐት በምድር አሳወቁ ፣ ለሀገራቸው ሲሉ መስዕዋት ሆኑ ፣ ለእሷ ሲሉ ህይወታቸውን ያለምንንም ስስት ገበሩ፣ ኧረ ስንቱን ልበል ጥበባቸው ስራቸው ተነግሮ አያልቅም።እነዚህ ሰዎች ኢትዮጵያውያን ናቸው።ተባሉ አንቺም ታሪክሽን እንኳ ሳታውቂ ኢትዮጵያዊ ነኝ አልሽ? መልሽልኝ።.......
✍bee
BY ሕይወትን - በገፅ
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/nibab_lehiwot/149